News & Stories
Latest Posts
![Ato Kassahun Follo Ato Kassahun Follo](https://cetu.et/wp-content/uploads/elementor/thumbs/1-qpjr3gv58an2v3sgtw5origcqat9drk2lissydal4g.jpg)
ካሳሁን ፎሎ ለቀጣዮቹ 3 ዓመታት የዓለም ሥራ ድርጅት የሚያስተዳድር አካል (Governing Body) አባል በመሆን ተመረጡ
በጀኔቫ ስዊዘርላንድ እየተካሄደ ባለው የዓለም ሥራ ድርጅት (ILO) 112ኛ ጉባኤ ሰኔ 3 ቀን 2016 ዓ.ም በተካሄደው ስብሰባ ለቀጣይ 3 ዓመታት በበላይነት የሚቆጣጠሩና የሚያስተዳድሩ አካላትን ከሠራተኞች ፣ከመንግሥታትና ከአሠሪዎች መካከል ለመምረጥ ባደረገው እንቅስቃሴ ካሳሁን ፎሎ የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ባገኙት ከፍተኛ ድምፅ የዓለም ሥራ ድርጅት የሚያስተዳድረው አካል (Governing Body) አባል በመሆን መመረጣቸውን ወደ ስፍራው ካቀኑ የኢሠማኮና የ9ኙ ኢንዱስትሪ ፌዴሬሽኖች የልኡካን ቡድን አባላት መረጃውን ሰምተናል።
በተመሳሳይ 112ኛ ጉባኤ ቅዳሜ ግንቦት 30 ቀን 2016 ባካሄደው ስብሰባው የዓለም ሥራ ድርጅትን በበላይነት Read More ከተለያዩ አባል ሀገራት የተውጣጡ የመንግሥት 28 አባላት ተወካዮች፣ አሠሪን የሚወክሉ 14 አባላት እና ሠራተኞችን የሚወክሉ 14 አባላት ያሉት የሚያስተዳድረው ይህ የበላይ አካል አባላት በየሶስት አመቱ በዓለም አቀፍ የሥራ ጉባኤ የሚመረጥ ሲሆን ከመንግሥት መቀመጫዎች ውስጥ አስሩ ዋና ዋና የኢንዱስትሪ ጠቀሜታ ባላቸው ሀገራት በቋሚነት የተያዙ ሲሆን የተቀሩት የመንግሥት መቀመጫዎች በመንግሥታት ተወካዮች ይመረጣሉ ። ድርጅቱን በበላይነት የሚያስተዳድረው (governing body) አባል ሀገራት የዓለም ሥራ ድርጅት (የILO) ዋና ሥራ አስፈፃሚ አካል ሲሆን የድርጅቱን ዋና ዳይሬክተር ምርጫን ጨምሮ በድርጅቱ ፖሊሲዎች፤ ፕሮግራሞችንና በጀት ላይ ለሚቀጥሉት 3 አመታት የሚወስን አካል ነው፡፡ ምርጫዎቹ ጉባኤው የአባል ሀገራቶች የመንግሥታት፣ የአሠሪና የሠራተኞች ተወካዮችን ያሳተፉ ሲሆን ቀደም ብለው በወጡ እና መጨመር ባለባቸው የዓለም ሥራ ድርጅት ድንጋጌዎች ላይ የሶስቱም አካላት፣ በተናጠልና በጋራ እየመከሩ ይገኛል። ይህም ሀገራችን በድርጅቱ ውስጥ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የድርጅቱን ሥራ በቅርብ ለመከታተልና ከድርጅቱ ተገቢውን ድጋፍ ለማግኘት ካለው ፋይዳ ባለፈ የአገራችንን ተደማጭነት በመጨመር የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ውክልና ከፍ በማድረግ የገፅታ ግንባታችንን እና የዓለም አቀፍ ግንኙነት ደረጃችንን ያሳድጋል የሚል እምነትን አሳድሯል። በሠራተኞች ተወካዮችና በመንግስታቶች መካከል በተደረገው የሚያስተዳድሩ አካል (Governing Body) ምርጫ የኮንፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት ካሳሁን ፎሎና የኢፌድሪ ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በከፍተኛ ድምፅ አባል ለመሆን ማሸነፋቸው ሀገራችን ይህን ከፍተኛ የዓለም ሥራ ድርጅትን ከሌሎች ጋር ሆና በሁለቱም አደረጃጀት መሪ ሆኖ መመረጥ ትልቅ ፋይዳና ተጠቃሚነታችንን ሊያጎላ ይችላልና እንኳን ደስ ያለን ሲሉ ልኡካኑ ስሜታቸውን አስተላልፈዋል። የሚያስተዳድረው አካል የዓለም ሥራ ድርጅት ዋና ዳይሬክተርን ከመሾም ጀምሮ፣ የዓለም ሥራ ድርጅት ስምምነቶችን እና በአባል ሀገራት የተሰጡ ምክሮችን አፈፃፀም የሚገመግምና የዓለም አቀፍ የሥራ ደረጃዎችን መጣስ በተመለከተ የሚቀርቡ ቅሬታዎችን የሚመለከት ወሳኝ አካል ነው፡፡ የዓለም ሥራ ድርጅት የበላይ አካል ማኅበራዊ ፍትህን ለማስፋፋት እና በአለም አቀፍ የሥራ ሁኔታዎችን ለማሻሻል ድርጅቱ የሚያደርገውን ጥረት በመምራት ረገድ ወሳኝ ሚናም ይጫወታል። የሶስትዮሽ ውክልና ማለትም የመንግሥታት፣ የአሠሪዎች እና የሠራተኞች ድምጽ ሁሉም በውሳኔ አሰጣጡ ሂደት ውስጥ መወከሉንም ያረጋግጣል።
![44 44](https://cetu.et/wp-content/uploads/elementor/thumbs/44-qnunbuy475agw5cm1cibg6p2soy4addd4ph15w7uyk.jpg)
![](https://cetu.et/wp-content/uploads/2024/05/55-1024x682.jpg)
![](https://cetu.et/wp-content/uploads/2024/05/10-2-1024x682.jpg)
ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር መወያየት እንደሚፈልጉ ሠራተኞች ተናገሩ
የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) ሚያዝያ 23 ቀን 2016 ዓ.ም. በኦሮሞ ባህል ማዕከል ባዘጋጀው ዓለምአቀፉ የሠራተኞች ቀን በዓል ላይ ታዳሚ የሆኑ ሠራተኞች የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ(ዶ/ር) በመላው አገሪቱ በየደረጃው የሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎችን አግኝተው ያነጋገሩ ቢሆንም ሠራተኛውን ግን እስካሁን ያላነጋገሩ በመሆኑ ጊዜ መድበው ከሠራተኛው ጋር ውይይት እንዲያደርጉ እንደሚፈልጉ ተናግረዋል፡፡ Read Moreበበዓሉ ላይ በነበረው የውይይት መርሀግብር ከተለያዩ ተቋማት የመጡ እነዚሁ ሠራተኞች እንዳነሱት የኢትዮጵያ ሠራተኞች በአገሪቱ ማኅበራዊ፣ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ግንባር ቀደም ተሳታፊ ናቸው፡፡ሠራተኛው በታማኝነት ግብሩን የሚከፍል ቢሆንም እውቅና እንኳን ለማግኘት ያልቻለ መሆኑን ተሳታፊዎች ተናግረዋል፡፡በኑሮ ውድነትና ሌሎች ችግሮች እየተሰቃየ የሚገኘውን ሠራተኛ ችግሩን በቅርበት ለማወቅና ለማነጋገር እንኳን መድረክ እንዳልተመቻቸለት አስቀምጠዋል፡፡ ተሳታፊዎቹ በተለይ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሚጠበቅበትን ድርሻ እየተወጣ እንዳልሆነ ቅሬታቸውን አሰምተዋል፡፡
እነዚህ ሠራተኞች የሚያጋጥሟቸውን ችግሮች ሁሉ አገራቸውን በማስቀደም ተቋቁመው እና ቅድሚያ ለአገራቸው ሰጥተው የሚገኙ ቢሆንም እነሱን ቀርቦ ያሉባቸውን ችግሮች ለመረዳትና ለማነጋገር ግን መድረክ ሊመቻች እንዳልተቻለ ቅሬታቸውን ገልጸዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ በተለያዩ መድረኮች ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር በመገናኘት ስላሉ ችግሮች ሲወያዩና መፍትሔ ሲፈልጉ የሚታይ ቢሆንም የሠራተኛውን ክፍል ግን ሊያገኙት አለመቻላቸው እንዳሳሰባቸው አስረድተዋል፡፡
በዚህ በዓል የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ፣የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈርያት ካሚል፣የሁለቱ አሠሪዎች ኮንፌዴሬሽንና ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንቶች እንዲሁም የዓለም ሥራ ድርጅት ተወካይ ንግግር አድርገዋል፡፡ በቀጣይ የ‹‹ሠራተኛው ድምጽ›› እትማችን በዓሉን በተመለከተ ሰፊ ዘገባ ይዘን የምንቀርብ መሆኑን ከወዲሁ እንገልጻለን፡፡
እነዚህ ሠራተኞች የሚያጋጥሟቸውን ችግሮች ሁሉ አገራቸውን በማስቀደም ተቋቁመው እና ቅድሚያ ለአገራቸው ሰጥተው የሚገኙ ቢሆንም እነሱን ቀርቦ ያሉባቸውን ችግሮች ለመረዳትና ለማነጋገር ግን መድረክ ሊመቻች እንዳልተቻለ ቅሬታቸውን ገልጸዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ በተለያዩ መድረኮች ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር በመገናኘት ስላሉ ችግሮች ሲወያዩና መፍትሔ ሲፈልጉ የሚታይ ቢሆንም የሠራተኛውን ክፍል ግን ሊያገኙት አለመቻላቸው እንዳሳሰባቸው አስረድተዋል፡፡
በዚህ በዓል የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ፣የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈርያት ካሚል፣የሁለቱ አሠሪዎች ኮንፌዴሬሽንና ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንቶች እንዲሁም የዓለም ሥራ ድርጅት ተወካይ ንግግር አድርገዋል፡፡ በቀጣይ የ‹‹ሠራተኛው ድምጽ›› እትማችን በዓሉን በተመለከተ ሰፊ ዘገባ ይዘን የምንቀርብ መሆኑን ከወዲሁ እንገልጻለን፡፡
![Women](https://cetu.et/wp-content/uploads/2024/02/1-1024x512.png)
![CETU logo](https://cetu.et/wp-content/uploads/2024/02/LOGO-300x300.jpg)
"ኮንቬንሽን 189፣ 190፣ 97 እና 143 ለተጋላጭ የቤት ሠራተኞች፣ፍልሰተኞች ሠራተኞች፣ እና በሥራ ቦታ ጥቃት እና ትንኮሳ ሰለባዎች ኑሮ ለሚኖረው አዎንታዊ ለውጥ ይደግፉ!ያግዙ! ያጽድቁ!!!"
የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ)“ኮንቬንሽን 189፣ 190፣ 97 እና 143 ለተጋላጭ የቤት ሠራተኞች፣ ፍልሰተኞች ሠራተኞች፣ እና በሥራ ቦታ ጥቃት እና ትንኮሳ ሰለባዎች ኑሮ ለሚኖረው አዎንታዊ ለውጥ ይደግፉ!ያግዙ! ያጽድቁ!!! በሚል መሪ ቃል ኮንቬንሽኖቹ ጸድቀው የአገሪቱ የሕግ አካል እንዲሆኑ እና ተግባራዊ እንዲደረጉ የሚያስችል የግንዛቤ ፈጠራ የካቲት 12 ቀን 2016 ዓ.ም. በኢንተርሌግዠሪ ሆቴል ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ሕግ አውጪዎች፣የዓለም ሥራ ድርጅት ተወካይ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች፣የአሠሪ ተወካዮች ሚዲያዎችና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት እንደሚያደርግ አስታወቀ።
ምንም እንኳን በመደበኛው ዘርፍ Read More
ሌላው በኢሠማኮ በኩል የይጽደቅ ውትወታ የሚደረግበት ፆታ ላይ የተመሰረተ ጥቃትን ጨምሮ በሥራ ቦታ የሚደርሱ ጥቃት እና ትንኮሳ መግታት ይረዳል የተባው የዓለም ሥራ ድርጅት ኮንቬንሽን 190 ነው፡፡ፆታ ላይ የተመሰረተ ጥቃት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሶስቱ ሴቶች አንዷን ሰለባ በማድረግ ወረርሽኝ ሆኖ የቀጠለ ነው። በኢትዮጵያም ቢሆን በሥራው ዓለም የሚፈጸመው ጥቃት እና ትንኮሳ አሳሳቢ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶችም ያሉት ነው። በከተማ እና በገጠር አካባቢዎች ጭምር ተጽእኖ በማድረግ በተለያዩ ዘርፎች መሰረታዊ ተግዳሮት ሆኖ ቀጥሏል።
የሥራ ቦታ ጥቃትን በስፋት ለመፍታት ኢሠማኮ የዓለም ሥራ ድርጅት ኮንቬንሽን 190 እንዲፀድቅ ጥሪ ያቀርባል። ይህ ኮንቬንሽን ኢትዮጵያ ሕገ–መንግሥታዊ ግዴታዋን እንድትወጣ፣ ዓለም አቀፋዊ ገጽታዋን እንድትገነባ፣ በሥራ ቦታ ያሉ ችግሮችን እንድታስቆም እና ለአገራዊ ተወዳዳሪነትና ለኢንዱስትሪ ልማት የበኩሏን አስተዋጽኦ እንድታበረክት ያስችላል።
በድህነት፣ለልማት መነሳሻ የሐብት ምንጭ እጥረት፣የአየር ንብረት መለዋወጥና የተፈጥሮ ውድመት፣ የተራዘሙና የማያቋርጡ ግጭቶችና መሰል በሆኑ በተለያዩ ገፊና እና ሳቢ ምክንያቶች በብዙ መቶ ሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ከአገር ለራሳቸውና ለቤተሰባቸው ገቢ ለማመንጨት፣የተሻለ ሕይወት ፍለጋ፣ለቴክኖሎጂና ትምህርት ተደራሽ ለመሆን፣አሳሳች መረጃዎችን በመቀበልና ቤተሰቦቻቸውን ለመገናኘት ወደ ሌላ አገር እንደሚፈልሱ ይታወቃል፡፡ከ15-29 በሚደርስ የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙትና ከ78 በመቶ በላይ የሆነውን ድርሻ የሚወስዱት እነዚህ ወጣቶች ፍልሰተኛ ሠራተኞች ለኢትዮጵያ መልካም እድል ወደ ሀገር ውስጥ በሚላከው ገንዘብ ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያደርጋሉ። ይሁን እንጂ በመዳረሻ አገሮች ብዙ ጊዜ ብዝበዛ፣ አድልዎ እና ደህንነቱ ያልተጠበቀ የሥራ ሁኔታ ያጋጥማቸዋል። በምላሹ፣ ኢሠማኮ በፍልሰተኛ ሠራተኞች ላይ የዓለም ሥራ ድርጅት ኮንቬንሽኖች 97 እና 143 እንዲፀድቁ ኢሠማኮ ይጠይቃል።
እንቅስቃሴውን
ይቀላቀሉ፣ ምቹ ሥራን ይደግፉ
ኢሠማኮ
ይህን ተፅዕኖ ያለው የውትወታ( የግንዛቤ ፈጠራ) ዘመቻ ሲያስተዋውቅ፣ ጥሪው ግልጽ ነው፡ የተጋላጭ ሠራተኞችን መብቶች የሚያስጠብቁ የዓለም ሥራ ድርጅት ኮንቬንሽኞች እንዲጸድቁ ለማስቻል እንቅስቃሴውን ይቀላቀሉ።
የዚህ ዘመቻ ስኬት በጋራ ድርጊቶች፣ የፖሊሲ ለውጥ እና ለሁሉም ፍትሃዊ እና ክብር ያለው የሥራ ቦታ መፈጠር ቁርጠኝነት ላይ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ ምቹነት ላለው ሥራ እና ፍትሃዊ የሆነ የሠራተኞች ገጽታን ለመፍጠር በጋራ እንነሳ።
![](https://cetu.et/wp-content/uploads/2023/12/0X3A8639-600x400.jpg)
በኢሠማኮ በተዘጋጀው የሠራተኞች መረጃ መለዋወጫ የህብረት ፕላት ፎርም የግንኙነት መተግበሪያ አጠቃቀም ላይ ስልጠና ተሰጠ
ሠራተኞች ከፌዴሬሽኖችና ከኢሠማኮ ጋር (on line) መረጃዎችን የሚለዋወጡበትና ሠራተኛው ችግር ሲያጋጥመው ልዩ ልዩ ድጋፎች ለማግኘት መረጃ የሚለዋወጥበት ህብረት ፕላት ፎርም (Union Plat form) የተሰኘውን የግንኙነት መተግበሪያ ተግባር ላይ ለማዋል ከምግብ መጠጥና ትምባሆ ኢንዱስትሪ ፌዴሬሽን ስር ከሚገኙ አሥር መሰረታዊ የሠራተኛ ማኅበራት ለተውጣጡ ተወካዮች ዛሬ ታህሳስ 9 ቀን 2016 ዓ.ም ስልጠና ተሰጠ፡፡የአትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አያሌው አህመድRead More
ስልጠናውን የሰጡት የኢሠማኮ የዕውቀት ቅመራና የአይሲቲ ባለሙያ አቶ ጋዲሳ ከበደ ማህበራቱ የአባላቶቻቸውን መረጃ አንድ ጊዜ ካስገቡ ሠራተኞቹ ሲስተሙን በመጠቀም የሚልኩትን መረጃ የፌዴሬሽኑም ሆነ የኢሠማኮ አመራሮች በመመልከት በቀላሉ መፍትሄ ለመፈለግ የሚያስችል በመሆኑ አሁን ስልጠናውን የወሰዱት ተወካዮች በቀጣይ ወደ የማኅበሮቻቸው በመሄድ ለአባላቶቻቸው ስለአጠቃቀሙ ገለጻ በማድረግ ሲስተሙን እንዲጠቀሙ ለማድረግ እንደሚረዳቸው ገልጸዋል፡፡
ስልጠናውን የወሰዱት የሠራተኛ ማህበራት ተወካዮች ከአዋሽ ወይን ጠጅ፣ከሞሐ ፐላንት፣ከሞሐ ተክለሀይማኖት፣ ከሞሐ ሰሚት፣ከኢስት አፍሪካ ቦትሊንግ፣ ከቃሊቲ ምግብ አክሲዮን ማህበር፣ ከጊፍቲ ምግብ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግ.ማህበር፣ ከፋፋ ምግብ አክሲዮን ማህበር፣ ከሄኒከን ቢራ እና ከብሔራዊ አልክሆል ፋብሪካ መሰረታዊ የሠራተኛ ማኅበራት የተውጣጡ የሠራተኛው ተወካዮች መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ኤች አይ ቪ/ኤድስ/ እንደሌለ በመቆጠሩ ከባድ መዘናጋት እየታየ መሆኑ ተገለጸ
ኤች አይ ቪ/ኤድስ/ እንደሌለ በመቆጠሩ ከባድ መዘናጋት እየታየ መሆኑ የተገለጸው የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን /ኢሠማኮ/ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ከዓለም ሥራ ድርጅት ጋር በመተባበር በየዓመቱ የሚከበረውን የፀረ ኤች አይ ቪ/ኤድስ/ቀን ህዳር 25 ቀን 2016 ዓ.ም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዳራሽ ባከበረበት ወቅት ነው፡፡
በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ36ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ
ለ35ኛ
ጊዜ "የማኅበረሰብ መሪነት ለላቀ ኤች አይቪ መከላከል' በሚል መሪ ቃል ሲከበር፤
የኢሠማኮ የማህበራዊ ጉዳይ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፍስሀፅዮን ቢያድግልኝ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር በኤች አይቪ ዙሪያ በነበረው የተዛባ
አመለካከት የተነሳ Read More በመርሀ-ግብሩ የኤች አይቪ/ኤድስ/ ቀንን ለምን እናከብራለን በሚል ርዕስ
ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀረቡት የኢሠማኮ ማኅበራዊ ጉዳይ ባለሙያ ወ/ሮ ሰርካለም ሽፈራው ስለ በሽታው ያለንን ግንዛቤን ለማሳደግ እና ሁሉም ዜጋ ከኤች አይ ቪ
የመጠበቅ ፣የመመርመር ህክምና እና እንክብካቤ የማግኘት መብት እንዳለው ግንዛቤ ለመፍጠር መሆኑን ገልጸው፤ በአሁኑ
ወቅት በሀገራችን ያለውን የኤች አይቪ/ኤድስ/ ስርጭት በሚመለከትም ቁጥሩ የቀነሰ ቢመስልም የመመርመርና ራስን የማወቅ ሁኔታው በጣም ስለቀነሰ በማህበረሰቡ ውስጥ ከፍተኛ
መዘናጋት አለ ብለዋል፡፡ በሌላ
በኩል የሥራና ክህሎት ሚኒስቴርን ወክለው በዕለቱ መልእክታቸውን ያስተላለፉት አቶ አብነት ፍቃዱ ኤች አይ ቪ ኤድስን ለመከላከል
የመንግሥት፣ የማኅበረሰቡና የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ አክለውም ከኢኮኖሚ፣ ከባህልና ከህግ ተፈጻሚነት አንጻር
የሚታየውን ኢፍትሀዊነት መቅረፍ እንደሚገባ አብራርተዋል፡፡ የበሽታውን ስርጭት ዓለማቀፋዊ ገጽታ ስንመለከት 38.4 ሚሊየን ሰዎች
ቫይረሱ በሰውነታቸው የሚገኝ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 25.6 ሚሊየን ወይም 66% የሚሆኑት በአፍሪካ ውስጥ እንደሚገኙ መረጃዎች ያሳያሉ
ብለዋል፡፡ በመርሀ-ግብሩ
በመገኘት የህይወት ልምዳቸውን ያካፈሉት ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ የሚገኘው
ወ/ሮ አዲስ ኪዳን አስፋው ማኅበረሰቡ ስለ በሽታው በቂ ግንዛቤ ያለው ቢሆንም ተመርምሮ ራሱን ለማወቅ ያለው ተነሳሽነት ዝቅተኛ
መሆኑን እና አሁንም አድሎና ማግለሉ እንዳለ መሆኑን በተለያየ ጊዜ ያገጠማቸውን ገጠመኝ በማንሳት ገልጸዋል፡፡
የ2016 ዓ.ም ኢትዮጵያ የዓለም የሥራ ድርጅት አባል የሆነችበት አንድ መቶኛ ዓመት በዓል እና የአሠሪና ሠራተኛ ጉባዔ ከደቂቃዎች በፊት በኃይሌ ግራንድ ሆቴል በይፋ መካሄድ ጀምሯል
![](https://cetu.et/wp-content/uploads/2023/12/13-1024x682.jpg)
![](https://cetu.et/wp-content/uploads/2023/12/3-1024x682.jpg)
![](https://cetu.et/wp-content/uploads/2023/12/5-1024x682.jpg)