News & Stories

Latest Posts

Ato Kassahun Follo
ካሳሁን ፎሎ ለቀጣዮቹ 3 ዓመታት የዓለም ሥራ ድርጅት የሚያስተዳድር አካል (Governing Body) አባል በመሆን ተመረጡ

በጀኔቫ ስዊዘርላንድ እየተካሄደ ባለው የዓለም ሥራ ድርጅት (ILO) 112 ጉባኤ ሰኔ 3 ቀን 2016 . በተካሄደው ስብሰባ  ለቀጣይ 3 ዓመታት በበላይነት የሚቆጣጠሩና የሚያስተዳድሩ አካላትን ከሠራተኞች ፣ከመንግሥታትና ከአሠሪዎች መካከል ለመምረጥ ባደረገው እንቅስቃሴ  ካሳሁን ፎሎ  የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ባገኙት ከፍተኛ ድምፅ የዓለም ሥራ ድርጅት የሚያስተዳድረው አካል (Governing Body) አባል በመሆን መመረጣቸውን ወደ ስፍራው ካቀኑ የኢሠማኮና 9 ኢንዱስትሪ ፌዴሬሽኖች የልኡካን ቡድን አባላት መረጃውን ሰምተናል።

በተመሳሳይ 112 ጉባኤ ቅዳሜ ግንቦት 30 ቀን 2016 ባካሄደው ስብሰባው የዓለም ሥራ ድርጅትን በበላይነት Read More

44

ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር መወያየት እንደሚፈልጉ ሠራተኞች ተናገሩ
የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) ሚያዝያ 23 ቀን 2016 ዓ.ም. በኦሮሞ ባህል ማዕከል ባዘጋጀው ዓለምአቀፉ የሠራተኞች ቀን በዓል ላይ ታዳሚ የሆኑ ሠራተኞች የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ(ዶ/ር) በመላው አገሪቱ በየደረጃው የሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎችን አግኝተው ያነጋገሩ ቢሆንም ሠራተኛውን ግን እስካሁን ያላነጋገሩ በመሆኑ ጊዜ መድበው ከሠራተኛው ጋር  ውይይት እንዲያደርጉ እንደሚፈልጉ ተናግረዋል፡፡ Read More

Women
CETU logo

"ኮንቬንሽን 189፣ 190፣ 97 እና 143 ለተጋላጭ የቤት ሠራተኞች፣ፍልሰተኞች ሠራተኞች፣ እና በሥራ ቦታ ጥቃት እና ትንኮሳ ሰለባዎች ኑሮ ለሚኖረው አዎንታዊ ለውጥ ይደግፉ!ያግዙ! ያጽድቁ!!!"

የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ)“ኮንቬንሽን 189፣ 190፣ 97 እና 143 ለተጋላጭ የቤት ሠራተኞች፣ ፍልሰተኞች ሠራተኞች፣ እና በሥራ ቦታ ጥቃት እና ትንኮሳ ሰለባዎች ኑሮ ለሚኖረው አዎንታዊ ለውጥ ይደግፉ!ያግዙ! ያጽድቁ!!! በሚል መሪ ቃል ኮንቬንሽኖቹ  ጸድቀው  የአገሪቱ የሕግ አካል እንዲሆኑ እና ተግባራዊ እንዲደረጉ የሚያስችል የግንዛቤ ፈጠራ የካቲት 12 ቀን 2016 ዓ.ም. በኢንተርሌግዠሪ ሆቴል ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ሕግ አውጪዎች፣የዓለም ሥራ ድርጅት ተወካይ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች፣የአሠሪ ተወካዮች ሚዲያዎችና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት እንደሚያደርግ አስታወቀ።

ምንም እንኳን በመደበኛው ዘርፍ Read More

በኢሠማኮ በተዘጋጀው የሠራተኞች መረጃ መለዋወጫ የህብረት ፕላት ፎርም የግንኙነት መተግበሪያ አጠቃቀም ላይ ስልጠና ተሰጠ

ሠራተኞች ከፌዴሬሽኖችና ከኢሠማኮ ጋር (on line) መረጃዎችን የሚለዋወጡበትና ሠራተኛው ችግር ሲያጋጥመው  ልዩ ልዩ ድጋፎች ለማግኘት መረጃ የሚለዋወጥበት  ህብረት ፕላት ፎርም (Union Plat form) የተሰኘውን የግንኙነት መተግበሪያ ተግባር ላይ ለማዋል ከምግብ መጠጥና ትምባሆ ኢንዱስትሪ ፌዴሬሽን ስር ከሚገኙ አሥር መሰረታዊ የሠራተኛ ማኅበራት ለተውጣጡ ተወካዮች ዛሬ ታህሳስ 9 ቀን 2016 ዓ.ም ስልጠና ተሰጠ፡፡የአትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አያሌው አህመድRead More



ኤች አይ /ኤድስ/ እንደሌለ በመቆጠሩ ከባድ መዘናጋት እየታየ መሆኑ ተገለጸ

ኤች አይ /ኤድስ/ እንደሌለ በመቆጠሩ ከባድ መዘናጋት እየታየ መሆኑ የተገለጸው የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን /ኢሠማኮ/ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ከዓለም ሥራ ድርጅት ጋር በመተባበር በየዓመቱ የሚከበረውን  የፀረ ኤች አይ /ኤድስ/ቀን ህዳር 25 ቀን 2016 ዓ.ም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዳራሽ ባከበረበት ወቅት ነው፡፡

በዓለም አቀፍ ደረጃ 36 ጊዜ በሀገራችን ደግሞ 35ኛ ጊዜ "የማኅበረሰብ መሪነት ለላቀ ኤች አይቪ መከላከል' በሚል መሪ ቃል ሲከበር፤ የኢሠማኮ የማህበራዊ ጉዳይ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፍስሀፅዮን ቢያድግልኝ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር በኤች አይቪ ዙሪያ በነበረው የተዛባ አመለካከት የተነሳ Read More


የ2016 ዓ.ም ኢትዮጵያ የዓለም የሥራ ድርጅት አባል የሆነችበት አንድ መቶኛ ዓመት በዓል እና የአሠሪና ሠራተኛ ጉባዔ ከደቂቃዎች በፊት በኃይሌ ግራንድ ሆቴል በይፋ መካሄድ ጀምሯል